Fati Ahmadin

Fati Ahmadin

Share

Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Fati Ahmadin, Health/Beauty, Dire, Addis Ababa.

24/07/2026

"ኢትዮጵያ በዓለም ተወዳድራ የላቀች ሀገር ለመሆን ካሉብን ዋነኛ ማነቆዎች ትልቁ ወደብ አልባነት ነው'"

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

24/07/2026
Photos from Harari Region Prosperity Party - ብልፅግና's post 24/07/2026
Photos from Harari Government communication affairs Office's post 23/07/2026
23/07/2026

የቁልቢ ገብርኤል በዓለ ንግስ በሰላም እንዲከበር አስፈላጊውን ዝግጅት መደረጉን ኮሚሽኑ አስታወቀ

በታላቅ ድምቀት የሚከበረው የቁልቢ ገብርኤል በዓለ ንግስ በሰላምና በደመቀ መልኩ እንዲከበር ለማስቻል የቅድመ ዝግጅቱን ተግባራት አጠናቆ ወደ ስራ መግባቱን የሀረሪ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ገለጸ።

የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ነገራ ዱፌራ እንደገለጹት በዓሉ በሰላምና በደመቀ መልኩ እንዲከበር ለማስቻል ለሁሉም ፈፃሚ አመራር እና አባላት እንዲሁም አጋዥ ተቋማት የበዓሉን አከባበር የተመለከተ የፀጥታ እቅድ ወቶ በቂ ግንዛቤ እንዲጨብጡ ከማድረግ ጀምሮ ሌሎች የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ሲሰሩ ቆይተዋል።

አሁን ወቅትም የበዓሉ አከባበር በሰላም እንዲጠናቀቅ አስፈላጊ የሰው ኃይል ተመድቦ ወደ ስራ መገባቱን ተናግረዋል።

ከበዓሉ ጋር ተያይዞ ወደ ከተማው የሚመጡ እንግዶች እና ነዋሪው አጠራጣሪ ጉዳዮች ሲያጋጥሙ ወድያውኑ ለፖሊስ ጥቆማ መስጠት ይኖርባቸዋል ብለዋል።

ምክትል ኮሚሽነር ነገራ አያይዘውም ሊደርሱ የሚችሉ የትራፊክ አደጋዎች ለመከላከል መላ አሽከርካሪዎች በትእግስት እና የመንገድ አጠቃቀም ህግና ስርዓትን ባከበረ መልኩ ማሽከርከር ይገባቸዋል ብለዋል።

ምክትል ኮሚሽነሩ ባስተላለፉት መልዕክት ሰላም ወዳዱ የክልሉ ሕዝብ እንደ ወትሮው ሁሉ ከፖሊስና ከሌሎች የፀጥታ ኃይሎች ጋር በጋራ እንዲሰራ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።

23/07/2026

በሀረሪ ክልል ከ200 ሺህ በላይ ዜጎች ነፃ የጤና ምርመራና ህክምና እየተሰጠ መሆኑ ተገለጸ

በሀረሪ ክልል ከ200 ሺህ በላይ ዜጎች ነፃ የጤና ምርመራና ህክምና አገልግሎት እየተሰጠ መሆኑ የክልሉ ጤና ቢሮ አስታወቀ።

የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት አካል የሆነው ነፃ የህክምና አገልግሎት "በጎነት ለጤናማ ማህበረሰብ" በሚል ሀሳብ ነው እየተሰጠ የሚገኝው።

የክልሉ ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር አብዲ አሚን እንደገለጹት እየተሰጠ የሚገኝው ነፃ የምርመራና የህክምና አገልግሎት አቅመ ደካማ ለሆኑ የሕብረተሰብ ክፍሎች ተጠቃሚ የሚያደርግ ነው።

ነፃ የህክምና አገልግሎቱ በበጎ ፍቃደኛ የጤና ባለሙያዎች አማካኝነት እየተሰጠ መሆኑን ጠቁመው አገልግሎቱም በመንግስትና በተመረጡ የግል ጤና ተቋማት እየተሰጠ መሆኑን ገልጸዋል።

እየተሰጡ ከሚገኙ የጤና ምርመራዎች መካከልም የስኳር ህመም፣ የደም ግፊት፣ ከአንገት በላይ፣ የቆዳና የአይን እና የልብ ሕመም ምርመራና ሕክምና እንዲሁም ሌሎች ተላላፊ እና ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች ይገኙበታል ብለዋል ከዚህ በተጨማሪም ከ5 ሺህ በላይ የደም ልገሳ መርሃ ግብሮች እንደሚካሄድ ገልጸዋል።

በምርመራው ወቅትም ተጨማሪ ህክምና ምርመራ የሚያስፈልጋቸው ዜጎች ወደ ሚመለከታቸው የጤና ተቋማት በመላክ አገልግሎቱን እንዲያገኙ እየተደረገ ይገኛል ነው ያሉት።

ከዚህ በተጨማሪም በዘመቻው ተላላፊ እና ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችን አስመልክቶ ለሕብረተሰቡ ግንዛቤ የመፍጠር ስራ እየተከናወነ መሆኑን ገልፀዋል።

ዘመቻው የጤና አገልግሎት ከመስጠት ባለፈ የህዝብን የጤና ንቃት ለማሳደግና የመረዳዳት ባህልን ለማሳደግ የላቀ አስተዋጽኦ እንዳለው ጠቁመዋል።

በመሆኑም ኅብረተሰቡ ይህንን በመገንዘብ የአገልግሎቱ ተጠቃሚ እንዲሆን ጥሪ አቅርበዋል።

Want your business to be the top-listed Beauty Salon in Addis Ababa?
Click here to claim your Sponsored Listing.

Category

Website

Address


Dire
Addis Ababa